የጤና ሚኒስቴር የስራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ የጤና ባለመያዎች 'በሐሰተኛ መረጃ የተወናበዱ' እና 'ጥፋትን ዓላማቸው ያደረጉ' ናቸው አለ
(መሠረት ሚድያ)- የጤና ሚኒስቴር ከደቂቃዎች በፊት በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ በሰጠው መግለጫ ከሰሞኑ የመብት እና የጥቅም ጥያቄ አንስተው ያሉ የጤና ባለሙያች ብዙዎቹ በሐሰተኛ መረጃ የተወናበዱ፣ ጥቂቶቹ ደግሞ ጥፋትን ዓላማቸው ያደረጉ ናቸው በማለት ከሷል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በመግለጫው 'ጥቂት' ባላቸው የማስተማሪያ የጤና ኮሌጆች እና ተቋማት በመደበኛ የሥራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ የተወሰኑ ባለሞያዎች እንዳሉ መረጃዎች እንደደረሱት ጠቅሶ ድርጊቱ የራስን ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወገን እና መላውን ማኅበረሰብ ከመጉዳት ባለፈ ከሞያ ሥነ ምግባር፣ ከሰብአዊነት አኳያ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው ብሏል።
መንግሥት መፍትሔ ለመስጠት ቀደም ብሎ የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ 1362 /2017 አጸድቆ ደንብና መመሪያዎችን በማውጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል፣ በጎ ኅሊና ያላቸው የጤና ባለሞያዎች ይህንን በመገንዘብ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ ጥሪ እናቀርባለን በማለት "በሥራ ገበታቸው ላይ ባልተገኙ እንዲሁም በጤና ተቋሙም ሆነ ከጤና ተቋሙ ውጭ ሆነው ሁከትና ብጥብጥ በሚፈጥሩት ላይ አስፈላጊ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ቀድመን እናሳውቃለን" በማለት ማስፈራርያ አዘል መልዕክት አስተላልፏል።
በሌላ በኩል የጤና ባለሙያዎች ማህበር ቦርድ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት ለማቆም ውሳኔ ላይ መድረሱ ታውቋል።
ከዚህ በፊት አንዳንድ የአስቸኳይ፣ ድንገተኛ እና ነፍስ አድን ህክምናዎች እንዳይቋረጡ ተደርጎ የከፊል ስራ ማቆም አድማ ተደርጎ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ በጤና ባለሙያዎች ላይ የሚደርሰው እስር እና እንግልት ባለመቆሙ ሙሉ በሙሉ ስራ ወደማቆም መሄዳቸውን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል፣ ለአተገባበሩም መርሀ ግብር ተዘጋጅቶ ተሰራጭቷል።
መረጃን ከመሠረት!




እረ የት ሀገር ነው የሚኖሩት እነዚህ ሰዎች!? ጉድ እኮ ነው እንዴዴዴዴዴ
እረ የት ሀገር ነው የሚኖሩት እነዚህ ሰዎች!? ጉድ እኮ ነው እንዴዴዴዴዴ