ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ የጦር ጄቶች በመቐለ ሰማይ ላይ ዛሬ መታየታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
(መሠረት ሚድያ)- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ተዋጊ ጄቶች ዛሬ ረፋድ ላይ በመቐለ ከተማ ሰማይ ላይ በዝቅተኛ ከፍታ ሲያንዣብቡ መታየታቸው በነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ስጋትና መደናገጥን ፈጥሯል።
የአይን እማኞች ለመሠረት ሚድያ ዛሬ እንደገለጹት የጄቶቹ ድምፅ የተሰማውና በረ…


