በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሚኖሩበት ህጋዊ ቤት 'መሬት ባንክ ገብቷል' ተብለው እድሳት፣ ሽያጭ እና ስም ማዞር መከልከላቸው ተሰማ
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ላይ የተለያዩ ቅሬታዎች ተደጋግመው ይነሳሉ፣ ከኦንላይን ሲስተሙ አለመስራት እስከ የኪስ ገንዘብ የሚጠየቅበት የሙስና አሰራር በብዙዎች ዘንድ ይነሳል።
አሁን የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተ…



