(መሠረት ሚድያ)- የአማራ የፖለቲካ እስረኞች ወንጀላቸውን ካመኑ እና በፊርማቸው ካረጋገጡ እንደሚፈቱ የቀረበውን ሀሳብ አንቀበልም ያሉ ግለሰቦች ተለይተው ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የመሠረት ሚዲያ ምንጮች ገለጹ።
የቀድሞው የአማራ ተማሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሲሳይ መልካሙ፣ በላይ ሲሳይ፣ ማረው ስለሺ እና ኮሎኔል ሰለሞን ተፈሪ በለሊት የተወሰዱት ታሳሪዎች ሲሆኑ ከአባ ሳሙኤል እስር ቤት ተለይተው መወሰዳቸው ታውቋል። እንደ ምንጮቻችን ገለጻ እስረኞቹ የተወሰዱት በኃይል ተይዘው ሲሆን እስካሁን አድራሻቸው አልታወቀም።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ወደ 1,300 የሚሆኑ የፖለቲካ እስረኞችን ራሳቸው ወንጀላቸውን መፈጸማቸውን አምነው እንዲፈርሙ ሲያግባቡ መቆየታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
በዚህም መሰረት የቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት አባል ካሳ ተሻገር (ዶ/ር)፣ የቀድሞው የኢዜማ ፓርቲ ሊቀመንበር ጫኔ ከበደ (ዶ/ር) እና ረዳት ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይንን ጨምሮ ሌሎች ወንጀል መፈጸማቸውን አምነው መንግስትን ይቅርታ መጠየቃቸው ታውቋል።
የፈጸምነው ወንጀል የለም በሚል አንፈርምም ያሉ 30 የፖለቲካ እስረኞች እና ጋዜጠኞች ናቸው። አሁን ላይ አንፈርምም ያሉ ታሳሪዎች ላይ ተመሳሳይ ድርጊት ሊፈፀም እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል።
መንግስት በመጪው አዲስ አመት የፖለቲካ እስረኞችን ለመልቀቅ መንግስት አቅዶ እየሰራ መሆኑን ሚድያችን መዘገቡ ይታወሳል። በቀረበው የይቅርታ ሰነድ ላይ የተካተተው ቀጥተኛ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል፦
"በአማራ ክልል ፅንፈኛው ቡድን በሚያደርገው ትግል ላይ መሳተፌ ስህተት መሆኑን በማመን መንግሥትንና ሕዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ። በክልሉ ለጠፋው ሕይወት (በአሀዝ ተጠቅሷል) እና ለወደመው ንብረት (በአሀዝ ተጠቅሷል) ኃላፊነት እወስዳለሁ። ሁለተኛ በእንዲህ ያለ ፀረ-ሰላም ተግባር እንደማልሳተፍ ቃል እየገባሁ፤ ይህንን አድርጌ ብገኝ መንግሥት ማንኛውንም እርምጃ እንዲወስድብኝ በፈቃዴ እፈርማለሁ!"
ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው፣ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና እና አቶ ዮሀንስ ቧያለውን ጨምሮ በርካታ እስረኞች ይህንን ሰነድ 'አንፈርምም' በማለት መለየታቸው ተረጋግጧል።
| መሠረት ሚድያ |



ብልፅግና ፓርቲ አፋኝ እና አረመኔው ሰው በላ
የአካይስቶች አንድነት ነው
የማፍያዎች ግሩፕ ፓርቲ ነው 4.
ይሄ መንግሰት የዲሞክራሲን አይን አጥፍቷል