ሙስሊሙ ኀብረተሰብ ከሀይማኖቱ እና ከትምህርቱ አንዱን እንዲመርጥ እየተገደደ እንደሆነ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ገለፀ
(መሠረት ሚድያ)- "የኢትዮጵያ ሙስሊሙን ኀብረተሰብ ከሀይማኖቱ እና ከትምህርቱ አንዱን እንዲመርጥ በማስገደድ ከትምህርት እና ሀገራዊ ተሳትፎ በማራቅ የሚመጣ ዘላቂ ልማት አይኖርም" በማለት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት መግለጫ አውጥቷል።
ምክር ቤቱ ባወጣው ባለ ሁለት ገፅ መግለጫ ላይ እንደጠቆመው የትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ የሙስሊም ተማሪዎችን ኢላማ ያረገ 'ትንኮሳ' እና 'የማሸማቀቅ ተግባር' እየፈፀመ ነው ብሏል።
"በአዲስ አበባ ከተማም ጥቂት የማይባሉ ተማሪዎች የዚህ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል" ያለው ምክር ቤቱ ድርጊቱ የሙስሊሙን ሀይማኖታዊ መብት ከመጣሱም በላይ የሀገሪቱን ሰላም የሚያደፈርስ አፍራሽ ተግባር ነው ብሎታል።
በመግለጫው ላይ እንደተጠቀሰው በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በሰላም እጦት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣት እና ታዳጊዎች ከትምህርት በተስተጓጎሉበት ሁኔታ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር በበኩሉ ሰበብ በመፍጠር በትምህርት ገበታ ላይ ያሉትን ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ለማስተጓጎል መነሳቱ አመራሩ ለማን እንደቆመ አጠያያቂ አርጎብናል ይላል።
"ሙስሊም ተማሪዎችን በሰላት እና በሂጃብ ሰበብ በማዋከብ ከትምህርት የማሰናከል ኢ-ሰብዓዊ ተግባር በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል" በማለት ህዝበ ሙስሊሙ የሙስሊም ተማሪዎችን ችግሮች ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች በሰላማዊ እና ህጋዊ መንገድ ብቻ ለመብቱ እንዲታገል ጥሪ አቅርቧል።
-መሠረት ሚድያ-





አህያውን ፈርቶ ዳውላውን
አብይ ኦሮሞ ሲሆን ሲመሰገን ፕ/ሮ ብርሃኑ የሌላ ብሔር ስለሆነ መወገዙ ግርም ይላል
ሙስሊሙ ለምን በሌላው ላይ የራሱን ሃይማኖት አለባበስ ይጫናል። ትምህርት ቤት neutral መሆን ይገባዋል።