ከሦስት ዓመታት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ በዋስ ተፈትቶ የነበረው ዶ/ር ሲሳይ አውግቼው ማረሚያ ቤት በር ላይ በድጋሜ ታሰረ
(መሠረት ሚድያ)- በአማራ ክልል ከተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ከተያዙ የፖለቲካ እስረኞች መሀል ዶ/ር ሲሳይ አውግቼው ይገኝበታል።
ለሦስት ዓመታት ያህል በእስር ላይ የቆየው ዶ/ር ሲሳይ በዛሬው ዕለት በዋስ ተፈትቶ ከእስር ቤት ሲወጣ በድጋሜ መታሰሩን መሠረት ሚድያ ከቤተሰብ እና ከማረሚያ ቤት ምንጮቹ አረጋግጧል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ የፀረ-ሽብር ወንጀል እና የሕገ-መንግሥት አንደኛ ምድብ ችሎት ዶ/ር ሲሳይ በመቶ ሺህ ብር ዋስ እንዲወጣ ብይን መስጠቱን ተከትሎ በዛሬው ዕለት ከቂሊንጦ ማረፊያ ማእከል ተፈትቶ ሲወጣ የፌደራል ፖሊስ በር ላይ ጠልፎ እንደወሰደው ታውቋል።
እስር ቤት በር ላይ ሲጠባበቁ የነበሩ ወዳጅ ዘመዶቹ በፌደራል ፖሊስ መዋከባቸው እና በርካታ የታጠቀ የመንግሥት ኃይል መንገድ ዘግቶ ዶ/ር ሲሳይን ከእስር እስኪወጣ እየተጠባበቀ እንደነበርም ሚድያችን ሰምቷል።
ቀደም ሲል በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረው ፍርድ ቤት በዋስ እንዲወጡ ብይን ከሰጠ በኋላ የፌደራል ፖሊስ፣ የፍትሕ ሚኒስቴር ዓቃቤያን ሕግ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አባላት በጋራ ሆነው ቂሊንጦ እስር ቤት በር ላይ በመጠበቅ በርካታ ዜጎችን አስረው መወሰዳቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
-መሠረት ሚድያ-




ስርዓት አልበኝነት የነገሰባት ሀገር ናት። ያሳዝናል አሁን በዚህ ስዓት የሁሉም ሰው ዋስ ጠበቃ መድሃኔ ዓለም ብቻ ነው።
በቅርቡ ዓመታት የፍትህ ስርዓታችን በከፍተኛ ፈተና ውስጥ ገብቷል። “ህግ እናስከብራለን” በሚል ስም የሚንቀሳቀሱ አካላት ራሳቸውን ከህግ በላይ በማድረግ የፍትህ መሠረታዊ መርሆችን እየጎዱ ነው። ህግ ለሁሉም እኩል መሆን ሲገባው፣ በአንዳንድ ጊዜ ግን በስልጣን ያሉ አካላት ፍርድ ቤቶችን እንኳን በማለፍ ውሳኔ ለመስጠት የሚሞክሩ ሁኔታዎች ታይተዋል።
ፖሊስ ዋና ተግባሩ ህግን ማስፈጸም እና ማህበረሰቡን መጠበቅ ነው፤ ነገር ግን ከፍርድ ቤት በላይ ልሆን የሚል አቋም ካሳየ ይህ የሥልጣን መጠን ማለፍ ነው። እንዲህ ያለ ሁኔታ በህግ ተወላጅ የሆነውን የፍትህ ሥርዓት ያደክማል፣ የህዝብ እምነትንም ያቀንሳል።
የፍትህ ሥርዓት እንዲጠናከር እና እንዲከበር የሚጠበቀው ሁሉም አካል በህግ ገደብ ውስጥ እንዲሰራ ነው። ህግ ከሰው በላይ ነው፤ ማንም አካል ከፍርድ ቤት ወይም ከህግ በላይ መሆን አይችልም። የህዝብ ድምፅ እንዲሰማ እና የፍትህ መርሆች እንዲጠበቁ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና የሕግ ክብር አስፈላጊ ናቸው።