ሚድያችን በቅርቡ የምርመራ ዘገባ ያቀረበበት መንግስታዊ ተቋም ዋና ስራ አስፈፃሚ እና ምክትሎቻቸው በዛሬው ዕለት በቁጥጥር ስር ዋሉ
(መሠረት ሚድያ)- በመስሪያ ቤቱ ውስጥ በሚከናወኑ ህገ ወጥ ድርጊቶች ዙርያ ሚድያችን በቅርቡ የምርመራ ዘገባ ያቀረበበት የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ (አይቲ ፓርክ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ዛሬ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።
ሚድያችን በሰራው ዘገባ "አይቲ ፓርክ" ተብሎ በሚጠራው ማእከል ውስጥ በዶላር እየከ…



