የሙዚቃ አቀናባሪ ካሙዙ ካሳ እና ጋዜጠኛ በሻቱ ቶለማርያም ብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት እጩ ሆነው ቀረቡ
(መሠረት ሚድያ)- የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዘንድሮው ምርጫ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት እንዲሁም ለክልል ምክር ቤቶች እጩዎቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
መሠረት ሚድያ የምርጫ ዘገባዎችን በተከታታይ ማቅረብ የሚቀጥል ሲሆን በዛሬው ዕለት የየካ ክፍለ ከተማ እጩዎችን ይዘን ቀርበናል።
ዛሬ የወጣ መረጃ እንደሚጠቁመው የሙዚቃ ባለሙያው ካሙዙ ካሳ ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ከየካ ክፍለ ከተማ ይወዳደራል።
ሰባተኛው አገራዊ ምርጫ አዳዲስ የብልፅግና እጩዎችን ማስተዋወቅ የቀጠለ ሲሆን የቀድሞ ጋዜጠኛ እና የኦዳ አዋርድ መስራችና አዘጋጅ በሻቱ ቶለማሪያም በተመሳሳይ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ብልፅግናን በመወከል ከየካ ክፍለ ከተማ ትወዳደራለች።
እነዚህን እጩዎች ለየት የሚያደርጋቸው ከዚህ በፊት የብልፅግና ፓርቲ አባል መሆናቸው በህዝብ ዘንድ የማይታወቅ መሆኑ ነው።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ እንዲሁ ከየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግናን ወክለው እንደሚወዳደሩ ታውቋል።
-መሠረት ሚድያ-


