ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከሰሞኑ ዲያስፖራዎችን በተመለከተ ያደረጉትን አወዛጋቢ ንግግር አስመልክቶ በሚድያ አስተያየት የሰጡ መምህር እና ጋዜጠኛ መታሰራቸው ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሰሞኑን “በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሲሟገቱ ይኖሩና ሲሞቱ መጥተው ቅበሩን ይላሉ” በማለት የተናገሩት ንግግር ብዙዎቹን አስቆጥቷል፣ መመጋገሪያም ሆኖ ቆይቷል።
ይህንን የዲያቆን ዳንኤል ንግግር በማውገዝ 'ነጋሽ' በተባለ የበይነ-መረብ ሚዲያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መምህር የሆኑት መምህር ሲሳይ አዳነ ተናግረው ነበር።
ውግዘቱን ተከትሎ የአዲስ አበባ ፖሊስ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም መምህር ሲሳይ አዳነን እና ቃለ-መጠይቅ ያደረገላቸውን ጋዜጠኛ ነጋሽ በዳዳን በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።
ሁለቱን እስረኞች ለመጎብኘት ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተለምዶ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ተብሎ ወደ ሚጠራው ማረፊያ ቤት ያቀኑት ሊቀ ትጉኃን መምህር ደረጀ ዘወይኔ የተባሉ ጠያቂም መታሰራቸውን ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ተናግረዋል።
ጋዜጠኛ ነጋሽ በምርመራ ወቅት የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ንግግር የተተቸበትን ቃለመጠይቅ ከዩትዩብ ላይ እንዲያወርድ መገደዱን እና ለእስር ያበቃው ይሄው የዲያቆኑ ንግግር እንዲወገዝ አመቻችተሀል በሚል መሆኑ ታውቋል።
እስረኞቹ በፌደራል አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረቡ ሲሆን መንግስት በሕዝብ ዘንድ አመኔታ እንዳይኖረው በመንግስት ላይ ማነሳሳት፣ በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ ሁከት እና ብጥብጥ ለመፍጠር ሞክረዋል በሚል ጠርጥሬያቸዋለሁ ሲል ፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ ጋዜጠኛ ነጋሽ በዳዳን የ50 ሺህ ብር ዋስ በማስያዝ በውጭ ሆኖ ጉዳዩን እንዲከታተል የበየነ ቢሆንም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጋዜጠኛውን ለመልቀቅ ፍቃደኛ ሳይሆን መቅረቱንም ምንጮች ለመሠረት ሚዲያ ጠቁመዋል።
ፍርድ ቤቱ ሁለቱን የቤተክርስቲያን መምህራንን ለተጨማሪ ምርመሪ ለአስር ቀናት በማረፊያ ቤት እንዲቆዩ አዟል።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) የቦርድ ሰብሳቢ ናቸው።
-መሠረት ሚድያ-




አብድ ማን እንበለው? አብድ አል አቢይ አሊ አህመድ?
ይች ሁከት ና ብጥብ የምትል ነገር አድሎ ተደርጎባታል:: ብዙ ሁከት ፈጣሪ በበዛበት...ወንጌል...