በነዳጅ ዘርፍ ላይ ከሚስተዋለው ስር የሰደደ ሙስና እና ዝርፊያ ጋር በተያያዘ ሚኒስትሩ ላይ ምርመራ እና ክትትል እንዲደረግ ተጠየቀ
(መሠረት ሚድያ)- ሰሞኑን በስፋት ከታየው የነዳጅ ግዥ፣ የስርጭት እጥረት እና መዛባት ጋራ በተገናኘ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን ሦስት ከፍተኛ ሓላፊዎች እንዲሁም 18 የሚደርሱ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ንግድ ጽሕፈት ቤት አመራሮች በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡
ሐላፊዎቹ…


