"እኔም የመንግስት ሰራተኞች የኑሮ ከብዶናል ጥያቄን በተመለከተ የማውቀውን እውነት ለማጋራት እፈልጋለሁ"- የዩኒቨርሲቲ መምህር ከከምባታ ዞን
(መሠረት ሚድያ)- ከመጋቢት 13-14/2014 ዓ.ም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር አመራሮች ከኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አመራሮች ጋር በመሆን በተለያዩ የመምህራን ጉዳዮች ላይ በትምህርት ሚኒስቴር ቢሮ ባለው ትንሹ አዳራሽ ተሰብስበን ነበር። በዕለቱ መድረክ የያዙት የትምህርት ሚኒስትሩ ነበሩ እና ከመምህራን የተነሱ አንኳር ጥያቄዎች:
ለዩኒቨርሲቲ መምህራን በተለይ ከመምህራን ማህበር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጣ ቡድን አጥንቶ ያቀረበው 3 አማራጮች ያሉት የደመዎዝ ማሻሸያ ይተግበርልን
መምህራን በሚኖሩባቸው ከተሞች ላይ ቤት መስሪያ ቦታ 100 ካሜ መሬት ይሰጠን
መሬቱ ከተሰጠን በኋላ ቤት መገንባት እንድንችል በአነስተኛ የወለድ መጠን ሰርተን የምንከፍለው የባንክ ብድር ይመቻችልን
የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ ላይ የተጣለው ከፍተኛ ታክስ(35%) ይቀነስልን
እንደሌሎቹ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች (Carrier Structure) ይተግበርልን የሚሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ነበሩ።
በሰዓቱ የተባልነው መምህራን ስራ አያቁሙ፣ ሁሉንም ተራ በተራ እንመልሳለን ስለዚህ ሄዳችሁ መምህራንን የማረጋጋት ስራ ስሩ ነበር፣ እስካሁን ግን ምንም የተቀየረ ነገር የለም።
በጣም የገረመኝ ነገር በሰዓቱ ከተጠኑት አማራጮች አንዱ እንደሚጸድቅ ቃል ከተገባ በኋላ 730 ብር ብቻ ጨምረው ቀለዱብን።
በማግስቱ ይሄ ለምን የሚል ጥያቄ በኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አማካኝነት ስናቀርብ የተሰጠን ምላሽ "ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለካቢኔያቸው አቅርበው ከተወያዩ በኋላ ከሶስቱ አማራጮች ሶስተኛውን እንኳን እናጽድቅ ብንል ለአመቱ ከተበጀተው በጀት 9ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ይፈልጋል፣ ይሄ ደግሞ ከሀገሪቱ አቅም በላይ ነው" በማለት መለሷቸው።
እግዜር ያሳያችሁ፣ እንግዲህ ብዙም ሳይቆይ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በ31 ቢሊዮን ብር ተሰራ ተባለ፣ ያኔ ግራ ገባን። ትውልድ ለሚገነባው መምህር አቅም የሌላት ሀገር ለዚህ 31 ቢልየን ብር ከየት አመጣች? ሁለተኛው እና ሶስተኛው ዙርስ ምን ያህል ቢሊዮን ወጥቶ ይሁን?
እኔ ባለሁበት ክልል አርሶ አደሮች የአፈር ማዳበሪያ አንድ ኩንታል በ8,000 ብር ገዝተው ለመዝራት ተገደዋል፣ ይሄን ያልቻሉ መሬታቸው ጦሙን ያድራል ወይም ያለማዳበሪያ መዝራት።
“አሁንም የጤና ባለሞያዎችም ጠንክረው አንድነታቸውን ጠብቀው እስከመጨረሻው ካልታገሉ የሚሰጣቸው ማደንዘዣ ነው እንጂ መፍትሔ አያገኙም”
አብዛኞቹ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች የአራት እና አምስት ወራት የመንግስት የሰራተኞች ደመወዝ አልተከፈለም፣ ነገር ግን በክልሉ ያሉ ከተሞች እያንዳንዳቸው በትንሹ ከ7ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የኮሪደር ልማት ስራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ፣ ይሄ ግፍ ነው ተወርቶ ተዘርዝሮም አያልቅም።
አሁንም የጤና ባለሞያዎችም ጠንክረው አንድነታቸውን ጠብቀው እስከመጨረሻው ካልታገሉ የሚሰጣቸው ማደንዘዣ ነው እንጂ መፍትሔ አያገኙም፣ ስለዚህ በጣም መጠንከር አለባቸው ለማለት እወዳለሁ።
የዩኒቨርሲቲ መምህር ነኝ ከከምባታ ዞን
መረጃን ከመሠረት!





Taxt የማይከፈልበትን የገንዘብ መጠን ከፍ ማድረግ ለምሳሌ 10,000 ብር ; ሲቀጥል 35% tax በጣም የተጋነነ ነው : ተቀጣሪ ሰራተኛ ትልቅ ነጋዴ የማይከፍለውን ግብር ነው እየከፈለ ያለው