ለዛሬ ጠዋቱ ሰልፍ ሲዘጋጁ የመድረክ መደርመስ አደጋ ካጋጠማቸው ታዳጊዎች መሀል ህይወታቸው ያለፈ መኖሩ ተሰማ
(መሠረት ሚድያ)- ዛሬ ጠዋት በመስቀል አደባባይ የተከናወነው ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ እና ትርዒት ለማቅረብ ሲለማመዱ የነበሩ ታዳጊዎች የመድረክ መደርመስ አደጋ እንዳጋጠማቸው ትናንት ምሽት መረጃ ማቅረባችን ይታወሳል።
የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን በማስመልከት የተካሄደው ሰልፍ ላይ ለመሳተፍ ልምምድ ሲያደርጉ የነበሩት ታዳጊዎች አደጋው ያጋጠማቸው ትናንት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በመስቀል አደባባይ መሆኑ ታውቋል።
በዚህ ዙርያ ዛሬ የደረሰን ተጨማሪ መረጃ እንደሚጠቁመው በአደጋው ተጎድተው ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከተወሰዱ ታዳጊዎች መሀል ቁጥራቸው በውል ያልታወቁት ህይወታቸው ያለፈ መሆኑን መሠረት ሚድያ ሰምቷል።
"ገና በለጋ እድሜያቸው ጎበዝ ጎበዝ ተማሪዎችን ከየትምህርት ቤታቸው በመምረጥ መንግስት ለጎበዝ ተማሪዎች ያዘጋጀው የጉብኝት ፕሮግራም አለ፣ ለሶስት ቀን ስለምትቆዩ ብርድ ልብስ እና አንሶላ ይዛችሁ ኑ ተብለው ስድስት ኪሎ ካምፓስ አስገብተዋቸው ነበር" ብለው ለሚድያችን ቃላቸውን የሰጡ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የመረጃ ምንጫችን ናቸው።
ምንጩ አክለውም "ከዛ አምስት ቀን ትቆያላችሁ፣ ቀጥሎ አስር ቀን ትቆያላችሁ፣ ብሎም በቃ ጳጉሜ ትሄዳላችሁ ካሏቸው በኋላ መውጣት አትችሉም በማለት ለአባይ ግድብ ምርቃት ትርዒት ታቀርባላችሁ ብለው ስልጠና አስጀምረዋቸው ነበር" ይላሉ።
ለአዲስ ዓመት በዓል ጭምር ታዳጊዎቹ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሳይሄዱ ተነጥለው ማሳለፋቸው የታወቀ ሲሆን ላለፉት 15 ቀናት መስቀል አደባባይ ላይ በእንጨት እስከ 18 ደረጃ በተሰራ መድረክ ልምምድ ሲያደርጉ መቆየታቸው ታውቋል።
"ብዙዎቹን በአዲስ አበባ ባሉ ሆስፒታሎች ከፋፍለው ነው የላኳቸው። እኔ በምሰራበት ሆስፒታል 45 ልጆች ተጎድተው የመጡ ሲሆን ከመጡት ውስጥ 11 የሚሆኑት የጀርባ አጥንት ስብራት፣ የእጅ አጥንት ስብራት እና የእግር አጥንት ስብራት ያጋጠማቸው ሲሆን ሌሎች መለስተኛ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸዋል" ብለው ለሚድያችን የተናገሩት አንድ የጤና ባለሙያ ናቸው።
ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች የተወሰዱ ሲሆን የሞት አደጋ ያጋጠማቸው እንዳሉ ተሰምቷል።
ወጣቶቹ የዛሬውን ሰልፍ ለማድመቅ በየወረዳው ካሉ ትምህርት ቤቶች የተሰባሰቡ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ትናንት ምሽት የመጨረሻ ልምምድ እያደረጉ በነበረበት ሰዓት የመድረክ መደርመስ አደጋው መድረሱ ታውቋል።
"ብዙ ሆስፒታሎች በአምቡላንስ ተጨናንቀው ነበር፣ በየሆስፒታሉ በርካታ የፀጥታ አካላት ፈሰዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናት እየዞሩ ተጎጂዎችን ሲጎበኙ ነበር" ያሉት ሌላኛው የመረጃ ምንጫችን ናቸው።
በዘውዲቱ ሆስፒታል የሚሰሩ አንድ የጤና ባለሙያ በአደጋው የተጎዱ በቁጥር ለመግለፅ የሚቸግራቸው ታዳጊዎች ወደ ከትናንት ምሽት 3:20 ጀምሮ መምጣታቸውን ገልፀዋል።
"የተለያየ የጉዳት መጠን ያላቸውን ወጣቶች ተቀብለናል" በማለት ተጨማሪ መረጃ አሁን ላይ መስጠት እንደማይችሉ ገልፀው ነበር።
"የልጆቹ ወላጆች በር ላይ እየተላቀሱ ነው" ያሉት አንድ የታዳጊ ዘመድ ብዙ ሰው ግራ ተጋብቶ ልጁን በመፈለግ ላይ ነበር ብለዋል።
በአደጋው ዙርያ እስካሁን በመንግስት አካላት የተባለ ነገር የለም።
-መሠረት ሚድያ-





ወላጆች ለአቅመአዳም / ለአቅመሄዋን ያልደረሱ ህጻናት ልጆቻቸዉን እነሱ መቆጣጠር በማይችሉበት ሁኔታ ለሳምንታት ዉጪ እንዲያድሩ መፍቀዳቸዉ ምን ማለት ነዉ? ይሄ ከባድ እንዝላልነት ነዉ! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እያሉ አይቻቸዋለሁ፣ አብዛናዎቹ እድሜአቸዉ ከ10 እስከ 12 ቢሆን ነዉ! የሚቆጣጠራቸዉ እና የሚጠብቃቸዉ ሳይኖር (በርግጥ የዩኒቨርስቲዉ ጥበቃዎች በየበራፉ አሉ) በግቢዉ ዉስጥ ሲራወጡ ነበር የሚዉሉት! ምግብም በደንብ እየቀረበላቸዉ የነብረ አይመስልም (ምክኒያቱም አንዳንድ ወላጆች ሳህን ሸክፈዉ ለልጆቻቸዉ ሲያቀብሉ አይቻለሁ)። የልጆቹ አያያዝ ፍጹም አሳፋሪና ሃላፊነት ይጎደለዉ ነብር! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በዚህ ህገወጥ ተግባር ዉስጥ ተባባሪ መሆኑ ፍጹም አሳፋሪ ነዉ!
Such massive negligence is nothing less than a green light for a class action lawsuit.
The parties that must be held accountable include:
The government
The city administration
GERD
The contractor who built the stage
Addis Ababa University
Are there any qualified and courageous lawyers in this country? This is your opportunity to prove to the nation—and to the world—that you stand for justice.
This is undeniably a class action case. All the entities above share responsibility, the real question is how much blame each party will carry. In other words: what percentage of liability will be assigned to each for this gross negligence?