(መሠረት ሚድያ)- የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በ2001 ዓ/ምያለባቸውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ለመንግስት ባቀረቡት ጥያቄና የወቅቱ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች ለጥያቄው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደረግ ለኦሮሚያ ክልል መንግስት ባቀረቡት የድጋፍ ጥያቄ መሰረት ከ200 በላይ የሚሆኑ የዩኒቨርሲቲው መምህራን የቤት መስሪያ ቦታ ከጅማ ከተማ በሊዝ ውል እንዲሰጣቸው ተፈቅዶ ነበር፡፡
በዚሁም መሰረት መምህራኑ የመጀመሪያውን የሊዝ ክፍያ ከፍለውና የሚጠበቅባቸውን ሌሎች ጉዳዮች አሟልተው ለእያንዳንዳቸው ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡
መሠረት ሚድያ ከጅማ የደረሰው መረጃ እንደሚያሳየው ምንም እንኳ መምህራኑ ከመጀመሪርያው የሊዝ ክፍያ በተጨማሪ የሚጠበቅባቸውን ዓመታዊ ግብር ላለፉት 17 ዓመታት ያለማቋረጥ እየከፈሉ ግዴታቸውን ቢወጡም ይዞታቸውን ማግኘት አልቻሉም፡፡
"በዚህም ምክንያት ቤቶቻችንን ገንብተን የመኖሪያ ቤት ችግራችንን መፍታት አልቻልንም። ምንም እንኳን በተደጋጋሚ ለችግራችን መፍትሄ እንዲሰጠን በተለያየ ወቅት ለከተማ አስተዳደሩ አቤቱታ ብናቀርብም ቀደም ሲል የነበሩትም ሆነ አሁን ያለው የከተማ አስተዳደር በወቅቱ ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ ወስዶ ቦታውን ለማስረከብ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል" ብለው መምህራኑ ለሚድያችን ተናግረዋል።
በዚህ ምክንያት የቦታው ነባር ባለይዞታ ባለቤቶች ነን የሚሉና ሌሎች ህገወጥ ሰዎች በቦታው ላይ ህገወጥ ግንባታ እንዲያካሂዱ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል፣ በዚህም ላይ የከተማ አስተዳደሩ ምንም እርምጃ ሳይወስድ ቀርቷል፡፡
"በመሆኑም ለዓመታት መፍትሄ ሳያገኝ የቆየው የፍትህ ማጣት ጩኽታችን አሁንም ሰሚ አጥቶ ቀጥሏል፣ ስለሆነም ጩኽታችንን ህዝብና የሚመለከታቸው አካላት ይወቁልን" በማለት መምህራኑ ለሚድያቸው ተናግረዋል።
በዚህ ዙርያ የከተማ አስተዳደሩን ለማረግ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፣ ቆይተው ምላሽ ካደረሱን ግን ይዘን እንመለሳለን።
መሠረት ሚድያ- የህዝብ ድምፅ!
ቆይ እስካሁን ባዶ መሬት ሳያለሙ ከያዙ ለሚያለማ መሰጠቱ ትክክል ነው ባይ ነኝ። 17 አመት ባዶ መሬት? የፒያሳው የአላሙዲን መሬትምኮ እርምጃ ተወስዶበት ነው አድዋ ሙዚየም የተሰራው።
የከተማ አስተዳደሩን ምላሽ ማካተት መልካም ነው
its unreadable...