የፖለቲካ እስረኞችን በአዲሱ አመት ለመፍታት መንግስት ታራሚዎች ይቅርታ እንዲጠይቁ እያግባባ መሆኑ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- በመጪው አዲስ አመት የፖለቲካ እስረኞችን ለመልቀቅ መንግስት አቅዶ እየሰራ መሆኑን የመሠረት ሚድያ ምንጮች ጠቆሙ፣ በቀረበ የይቅርታ ሰነድ ላይ 'አንፈርምም' ባሉ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ከወትሮው ለየት ያለ የከፋ አያያዝና ተደጋጋሚ ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ታውቋል።
በአማራ ክልል ከተቀሰቀሰው ግጭትና የደህንነት ሁኔታ ጋር ተያይዞ በርካታ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችና የሕዝብ ተወካዮች በቂሊንጦና በሌሎች ማረሚያ ቤቶች ታስረው እንደሚገኙ የሚታወቅ ነው።
"የአሁኑ የይቅርታ አፈታት ሂደት መነሻ ከስድስት ወራት በፊት የኢሰመኮ ኮሚሽነር አቶ ብርሃኑ አዴሎ ማረሚያ ቤቱን በጎበኙበት ወቅት የተገባው ቃል ነው" የሚሉት አንድ የመረጃ ምንጫችን በወቅቱ ኮሚሽነሩ ምርጫው ከተጠናቀቀ በኋላ ጉዳዩን በሽምግልና ለመፍታት እንደሚሞክሩ ቃል ገብተው ነበር ይላሉ።
በመቀጠልም በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ወደ ማረሚያ ቤቱ በድጋሚ በመመለስ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ዘንድ ፈቃድ ማግኘታቸውን በመግለጽ እስረኞቹ ተወካይ ኮሚቴ እንዲመርጡ ማድረጋቸው ተሰምቷል።
"ነገር ግን ንግግሮች ይደረጋሉ ተብሎ ሲጠበቅ መንግሥት ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጧል" ብለው ምንጫችን አስረድተዋል።
በቀረበው የይቅርታ ሰነድ ላይ የተካተተው ቀጥተኛ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል፦
"በአማራ ክልል ፅንፈኛው ቡድን በሚያደርገው ትግል ላይ መሳተፌ ስህተት መሆኑን በማመን መንግሥትንና ሕዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ። በክልሉ ለጠፋው ሕይወት (በአሀዝ ተጠቅሷል) እና ለወደመው ንብረት (በአሀዝ ተጠቅሷል) ኃላፊነት እወስዳለሁ። ሁለተኛ በእንዲህ ያለ ፀረ-ሰላም ተግባር እንደማልሳተፍ ቃል እየገባሁ፤ ይህንን አድርጌ ብገኝ መንግሥት ማንኛውንም እርምጃ እንዲወስድብኝ በፈቃዴ እፈርማለሁ!"
ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው እና አቶ ዮሀንስ ቧያለውን ጨምሮ በርካታ እስረኞች ይህንን ሰነድ 'አንፈርምም' በማለት መለየታቸው ተረጋግጧል። አንፈርምም ያሉ የ30 እስረኞች ሙሉ ዝርዝር የሚከተለው ነው፦
1. አቶ ዮሐንስ ቧያለው
2. ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ
3. ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው
4. መስከረም አበራ
5. ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ
6. ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃይለማሪያም
7. መሰረት ቀለመወርቅ
8. አለልኝ ምህረት
9. አባይ ዘውዱ
10. ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው
11. ጋዜጠኛ ገነት አስማማው
12. መንበር አለሙ
13. ማይክ መላከ
14. እስክንድር ሸፈራው
15. ሲሳይ መልካሙ
16. በላይ ሲሳይ
17. አሳምነው ታደሰ
18. መሰለ ቸሩ
19. አሱባለው በለሰ
20. ዶ/ር ዘሪሁን ባሕሪው
21. ኢ/ር ፍቅዱ ታፈረ
22. ሃሊማ መሐመድ
23. ሕይወት አለማየሁ
24. ጫኔ ዘየደ
25. ያሬድ ግርማ
26. ማረው ስለሺ
27. ታደሰ ወዳይነው
28. ሰለሞን ተፈሪ
29. ሙሉቀን ተስፋዬ
30. ደሳለኝ እጅጉ
በአሁኑ ወቅት በመንግሥት አካባቢ ያልፈረሙትን እስረኞች 'ምን እናድርጋቸው?' በሚለው ዙርያ ውይይቶች እየተደረጉ ይገኛሉ በማለት አንድ የመንግስት የመረጃ ምንጭ ለሚድያን ተናግረዋል።
ከይቅርታው በፊት የሦስት ወይም የሁለት ቀን ሥልጠና ለመስጠትና 'አይደገምም' የሚል ጽሑፍ ያለበት ቲሸርት ለማዘጋጀት ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ተገልጻል።
| መሠረት ሚድያ |



ብልፅግና ባስታጠቀው ታጣቂ
እኮ ነው ወገኖቻችን በግፍ የተገደሉት
የግፍ እስረኞች የምንም ሐላፊነት የመውሰድ
ግዴታ የለባቸውም
በግፍ የተገደሉት ወገኖቻችን እኮ
በብልፅግና ታጣቂዎች ሆኖ ሳለ
የግፍ እስረኞች ምንም አደረጉ